ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች
ተቃዋሚዎች
ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌ 4:5 " አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት።" ይላል። በዚህ አገላለፁ ቅዱስ ጳውሎስ እየነገረን ያለው የሃይማኖትን አንድነት (አንድ መሆኗን) አንጂ መብዛት እና መለያየት አይደለም። ለመሆኑ የቤተክርስቲያን አንድነት መቼ ተናጋ? በ257 አ.ም አርዮስ የተባለ መናፍቅ "ወልድ ፍጡር ነው።" የሚል የክህደት ትምህርቱን መንዛት ጀመረ። ይህ ሰው በወቅቱ በነበሩት ጳጳስ (ተፍፃሜተ ሰማዕት) ቅዱስ ጳውሎስ ተወግዞ ከቤተክርስቲያን አንድነት እንዲለይ ተደርጓል። ነገር ግን አኪላስ በተባለ አባት ከግዝቱ ተፈትቶ ከቤተክርስቲያን አንድነት ስለተጨመረ፣ የአርዮስ ክህደት አደባባይ መውጣት ጀመረ። አኪላስም ቀድሞ ግዝቱን እንዳይፈታ ከመምህሩ ቅዱስ ጳውሎስ ተነግሮት የነበረውን ቃሉን ሽሮ ዉግዘቱን በማንሳቱ ተቀስፎ ሞተ። ይህ የአርዮስ የክህደት ትምህርት ስር እየሰደደ በመምጣቱ በ325 አ.ም በንጉሥ ቁስጠንጢኖስ ዘመን ኒቂያ በተባለች ቦታ ላይ ትልቅ ጉባኤ ተደረገ። በጉባአዉም ላይ 318 ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አበው ተሰበሰቡ። አርዮስም በጉባኤው ላይ የኑፋዌ ትምህርቱን አሰማ። የትምህርቱም ይዘት ባጭሩ "ውልድ ፍጡር ነው። ነገር ግን ከሌሎች ፍጡር ይበልጣል። ለአብ ፍጡሩም ልጁም ነው። ኋላም በመዋዕለ ሥጋዌ ባሳየው ታዛዥነትና የተጋድሎ ፅናት ከእግዚአብሔር ቡራኬና ፀጋን ተቀብሎ አንደ ፃድቃን እንደ ሰማዕታት ሱታፌ አምላክነትን አገኘ።" የሚል ነው። ይህንንም የክህደት ትምህርት ያለምንም ማፈር በጉባኤው አሰማ። ቅዱስ አትናቴዎስ መፅሐፍ ቅዱስን መሰረት በማድረግ፣ ወልድ የአብ ፍጡር ሳይሆን ራሱ የፍጥረት ባለቤት መሆኑን፣እንደ አባቱ የስግደት እና የአምልኮ ባለቤት መሆኑን እና ሰውም ቢሆን ከአምላ...
ብዙ ውሽት ሲደጋገም እውነት ይመስላል ። ክፍል 2 '' መንግስት''
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ETV) ባለፍት ቅርብ ጊዜያት በእስላማዊ አክራሪነት ጠንቅ ላይ ያተኮረ 'ጥናታዊ ፊልም' በተከታታይ ሲያቀርብልን ፤ መንግስትም ደረስኩበት ያለውን ምስጢር ሲያጋልጥና ሕዝቡን ከእልቂት ለመከላከል ቀን ከሌት በትጋት እየሰራ መሆኑን ሲነገረን ሰነበተ ። መልካም ይህም ባልከፋ። ምንም እንኳ ከበርካታ አመትታት በፊት ቤተክርስቲያን በአክራሪ እስልምና አራማጆች በኩል የሚደርስባትን ጥቃት ለመንግስት እያሳወቀች ብትቆይም ፤ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ የነበረው መንግስት ፣ አሁን ነገሩ ወደርሱ ህልውና ሲመጣ እና ሲያነጣጥር 'ጉዳዩ ፣ ጉዳዬ ነው ፣ እኔንም ያገባኛል' ብሎ ይሄው እያራገበው ይገኛል። ቤተክርስቲያን ሲቃጠል፣ ምእመናን እና ካህናት በግፍ ሲታረዱ ፤ 'አላየሁም ፣ አልሰማሁም' ያለው መንግሥት አሁን አሁን እኔንም ያገባኛል ማለት ጀምሯል። ኢ.ቴ.ቪ. ያስተላለፋቸው በአክራሪነት ላይ ያተኮሩት እነዚህን ፊልሞች ሁሉኑንም ለመከታተል ሞክሬያለሁ። እንደመንግስት ማድረግ የሚገባውን እያደረገ ነው ስል ለራሴ ህሊናዬን ሞግቻለሁ። መንግስት ሀገር የሚመራ ፣ ኃላፊነት የሚሰማው አካል አድርጌ እረዳው ስለነበር በጥናታዊ ፊልሙ ውስጥ የቀረቡትን ስህተቶች ጭምር ስህተት ቢሆኑም በበጎ ጎኑ ለመቀበል ህሊናዬን ሳስጨንቅ ነበር። ነገር ግን ተደጋግመው የሚወጡት የዚህ ጥናታዊ ፊልም ዘገባዎች ስህተቱ ሆነ ተብሎ የታቀደበት ስህተት እንጂ እንዳጋጣሚ የሆነ እንዳልነበረ እያረጋገጡልኝ መጡ። ታሪክን ካለማወቅ የመጣ ሳይሆን እያወቁ የሚያጠፉ መሆኑን እየተረዳሁ መጣሁ። በመጨረሻም ግልጽ በሆነ ሁኔታ አቅጣጫን የማስቀየር ስራ እየሰሩ እንደሆነ ግልጽ ሆነልኝ።ይህም እንዲህ ነው። ባለፍት የኢ.ቴ.ቪ ተከታታይ 'ጥናታዊ ፊልሞች' ሰ...
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ