ልጥፎች

ከጃንዋሪ, 2014 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ሃገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ

ምስል

ብዙ ውሽት ሲደጋገም እውነት ይመስላል ። ክፍል 2 '' መንግስት''

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ETV) ባለፍት ቅርብ ጊዜያት በእስላማዊ አክራሪነት ጠንቅ ላይ ያተኮረ 'ጥናታዊ ፊልም' በተከታታይ ሲያቀርብልን ፤ መንግስትም ደረስኩበት ያለውን ምስጢር ሲያጋልጥና ሕዝቡን ከእልቂት ለመከላከል ቀን ከሌት በትጋት እየሰራ መሆኑን ሲነገረን ሰነበተ ። መልካም ይህም ባልከፋ። ምንም እንኳ ከበርካታ አመትታት በፊት ቤተክርስቲያን በአክራሪ እስልምና አራማጆች በኩል የሚደርስባትን ጥቃት ለመንግስት እያሳወቀች ብትቆይም ፤ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ የነበረው መንግስት ፣ አሁን ነገሩ ወደርሱ ህልውና ሲመጣ እና ሲያነጣጥር 'ጉዳዩ ፣ ጉዳዬ ነው ፣ እኔንም ያገባኛል' ብሎ ይሄው እያራገበው ይገኛል። ቤተክርስቲያን ሲቃጠል፣ ምእመናን እና ካህናት በግፍ ሲታረዱ ፤ 'አላየሁም ፣ አልሰማሁም' ያለው መንግሥት አሁን አሁን እኔንም ያገባኛል ማለት ጀምሯል። ኢ.ቴ.ቪ. ያስተላለፋቸው በአክራሪነት ላይ ያተኮሩት እነዚህን ፊልሞች ሁሉኑንም ለመከታተል ሞክሬያለሁ። እንደመንግስት ማድረግ የሚገባውን እያደረገ ነው ስል ለራሴ ህሊናዬን ሞግቻለሁ። መንግስት ሀገር የሚመራ ፣ ኃላፊነት የሚሰማው አካል አድርጌ እረዳው ስለነበር በጥናታዊ ፊልሙ ውስጥ የቀረቡትን ስህተቶች ጭምር ስህተት ቢሆኑም በበጎ ጎኑ ለመቀበል ህሊናዬን ሳስጨንቅ  ነበር። ነገር ግን ተደጋግመው የሚወጡት የዚህ ጥናታዊ ፊልም ዘገባዎች ስህተቱ ሆነ ተብሎ የታቀደበት ስህተት እንጂ እንዳጋጣሚ የሆነ እንዳልነበረ እያረጋገጡልኝ መጡ። ታሪክን ካለማወቅ የመጣ ሳይሆን እያወቁ የሚያጠፉ መሆኑን እየተረዳሁ መጣሁ። በመጨረሻም ግልጽ በሆነ ሁኔታ አቅጣጫን የማስቀየር ስራ እየሰሩ እንደሆነ ግልጽ ሆነልኝ።ይህም እንዲህ ነው። ባለፍት የኢ.ቴ.ቪ  ተከታታይ 'ጥናታዊ ፊልሞች' ሰ...

ብዙ ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል ክፍል 1. "ትውልዱ"

24/04/2006 ''ብዙ ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል'' ለሚለው ብሂል አይነተኛ ምሳሌ ያገኘሁለት ፈረንጆቹ ያከበሩት ያለፈው '' አዲስ ዓመት'' መግቢያ አካባቢ ነው፡፡ ይኸው የፈረደበት ''facebook'' በመልካም ምኞት መግለጫዎች ተጥለቅልቆ ነው የዋለው። በተለይ '' ኢትዮጵያውያን'' የሆኑት ጓደኞቼ! እኛ ኢትዮጵያውያን የራሳችን የሆነ ማንነት፣ ባህል እና ታሪክ ያለን ህዝቦች ነን፡፡ ዛሬ ''በስልጣኔ'' ወደኋላ ብትቀርም ፤ አንድ ወቅት በስልጣኔ ገናናነቷ የምትታወቅ ሀገር መሆኗን ዓለም እራሱ ሊያስተሃቅረው የማይችል ሀቅ ነው። ማን ያውቃል ነገ ደግሞ ዛሬ ሃያላን ነን የሚሉት ሃገራት ወድቀው ድሃ የተባሉት የተናቁት ሃገራት ደግሞ የሚነሱበት ጊዜ ይመጣ ይሆናል። በዚህ መነሳትና መውደቅ ውስጥ ታዲያ አንድን ሀገር ፣ ሀገር ሊያሰኙት የሚችሉት ፤ ታሪክ ፣ ማንነትና ባህል አብረው የሚጓዙ የሀገራት ህልውና ናቸው። እንደምረዳው ደግሞ ማንነት ፣ ባህል እና ታሪክ ከትውልድ ትውልድ ሊተላለፍ የሚችለው ያለው ትውልድ ማንነቱን ባህሉን እና ታሪኩን አክብሮ ሲይዘው አና ሲኖርበት ነው። ባህላችንን የማናከብር ፣ ማንነታችንን የማንጠብቅ ፣ በታሪካችን የማንኮራ ከሆነ ከኛ ለሚቀበለው ትውልድ ባህል ማንነት አና ታሪክ እቁብ የሚገቡ ነገሮች አይደሉም። ለርሱ ባህል ፣ ማንነት እና ታሪክ ሌላውን (ባእዱን) መከተል ብቻ ይሆናል። በየተሌቪዥን መስኮቱ የሚያየውን የነጮች ባህል ባህሉ ፣ ማንነት ማንነቱ እና ታሪክ ታሪኩ አድርጎ ይወስዳል። ይህ ትውልድ እነሆ ተፈጥሯል። የቤቶቻቸው ግድግዳዎች በነጮች ዘፋኞች እና የፊልም አክተሮች የተሞሉ '...